ይህ የብሉይ እና አዲስ ኪዳን መጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መምሪያና ማብራሪያ በቲም ፌሎስ የተጻፈ እና በኤስ አይ
ኤም ሥነ ጽሑፍ ክፍል በመጀመሪያ በ1989 ዓ.ም. የታተመ ነው፡፡ ማብራሪያው፣ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት
ውስጥ በተሰማሩ ሰዎች ላይ ትኩረት ከማድረጉ በተጨማሪ በግል የእግዚአብሔርን ቃል ለማጥናትም ሆነ በአዋቂዎች
የሰንበት ትምሕርት ቤት ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ ትምሕርት ቤት ለመጠቀም እንዲቻል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው፡፡
ማብራሪያው፣ መምሕርን ተክቶ ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ትምሕርተ-መለኮት ወይም አገልግሎት ለተማሪው ጠቃሚ
ትምሕርቶችን ያስተላልፋል፡፡