የመሐረነ አብ ጸሎትን ያዘጋጀው ከ40 መጻሕፍት በላይን የደረሰውና ካልዓይ ቅዱስ ያሬድ ፥ ካልዓይ ቄርሎስ
የተባለው ቅዱሱ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ ነው፡፡ ሲያዘጋጀውም ከተለያዩ ቅዱሳት መጻሕፍትና እንደ ቅዱስ ያሬድ
ካሉ ሊቃውንት ድርሰቶች ኀይለ ቃላት ያላቸውንና ለጸሎት ተስማሚ የሆኑ ቃላትን እንደ ንብ ቀስሞ ነው
ያዘጋጀው፡፡
፠ ቅዱሱ ያዘጋጀውም በመጽሐፈ ሰዐታት ድርሰቱ ላይ በስተመጨረሻ ከኪዳን በፊት እንዲደረስ አድርጎ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ከዓመት እስከ ዓመት በየዕለቱ ኪዳን በሚደርስባቸው ማንኛውም የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክንና ገዳማት ‹‹የመሐረነ አብ ጸሎት››ም ከኪዳን በፊት ይደርሳል፡፡
፠ የመሐረነ አብ ጸሎት ከኪዳን በፊት ብቻ ሳይሆን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት በዋይዜማው የሚደርስ፣ ለግል ጸሎት፣ ረሃብ ጦርነት፥ አባር ቸነፈር፥ ተስሕቦና ወረረሽኝ በሽታ እና የተለያዩ ችግሮች በመጡ ወቅት የሚደረስ ሲሆን ከእግዚኦታ ጋር አብሮ ስለሚባልም ‹‹የምሕላ ጸሎት›› በመባልም ይጠራል፡፡
፠ የጸሎቱ አደራረስም በመሪና በተመሪ (በቀኝና በግራ) በተራ ስለሆነ በጋራ የሚጸለይና ዜማው የሚመስጥ፤ የቃሉ አሰዳደርም የሚያስደንቅ፤ የያዘው ኀይለ ቃል እንባን የሚያስነባ ነው፡፡ በተለይም በገዳም ያሉ አባቶች በጋራ(በማኅበር)ና በግል ጸሎት ዕለት ዕለት ያደርሱታል፡፡
ይህን የጸሎት የምህላ ጸሎት ለምእመናን በቀላሉ እንዲያነቡት ፡ እንዲረዱት እንዲሁም ዜማውን እንዲለማመዱበት ታስቦ የተሰራ መተግበሪያ ነው።
፠ ቅዱሱ ያዘጋጀውም በመጽሐፈ ሰዐታት ድርሰቱ ላይ በስተመጨረሻ ከኪዳን በፊት እንዲደረስ አድርጎ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ከዓመት እስከ ዓመት በየዕለቱ ኪዳን በሚደርስባቸው ማንኛውም የኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክንና ገዳማት ‹‹የመሐረነ አብ ጸሎት››ም ከኪዳን በፊት ይደርሳል፡፡
፠ የመሐረነ አብ ጸሎት ከኪዳን በፊት ብቻ ሳይሆን፣ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት በዋይዜማው የሚደርስ፣ ለግል ጸሎት፣ ረሃብ ጦርነት፥ አባር ቸነፈር፥ ተስሕቦና ወረረሽኝ በሽታ እና የተለያዩ ችግሮች በመጡ ወቅት የሚደረስ ሲሆን ከእግዚኦታ ጋር አብሮ ስለሚባልም ‹‹የምሕላ ጸሎት›› በመባልም ይጠራል፡፡
፠ የጸሎቱ አደራረስም በመሪና በተመሪ (በቀኝና በግራ) በተራ ስለሆነ በጋራ የሚጸለይና ዜማው የሚመስጥ፤ የቃሉ አሰዳደርም የሚያስደንቅ፤ የያዘው ኀይለ ቃል እንባን የሚያስነባ ነው፡፡ በተለይም በገዳም ያሉ አባቶች በጋራ(በማኅበር)ና በግል ጸሎት ዕለት ዕለት ያደርሱታል፡፡
ይህን የጸሎት የምህላ ጸሎት ለምእመናን በቀላሉ እንዲያነቡት ፡ እንዲረዱት እንዲሁም ዜማውን እንዲለማመዱበት ታስቦ የተሰራ መተግበሪያ ነው።
Show More >